Posts

Showing posts from September, 2015

ሁሉም ሰው በእርግጠኝነት ንስሐ መግባት አለበት ክፍል አምስት (ሐ) All must repent

Image
ሁሉም ሰው በእርግጠኝነት ንስሐ መግባት አለበት ክፍል አምስት ( ሐ ) All must repent የእግዚአብሔርን መሠረታዊ እውነት ከተማረ እያንዳንዱ ሰው ንስሐ መግባት አለበት ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል 2 ኛ ጴጥሮስ 3 ፥ 9 There are no exceptions God wants everyone to repent   ታድያ ሰዎች ይህንን መረዳት አንድ ጊዜ እንዴት መቀበል ይችላሉ ? ለእግዚአብሔርስ እራሳቸውን ማስገዛትና ሕይወታቸውን መለወጥ እንዴት ይችላሉ ? ጳውሎስ ሐዋርያው ይህንን ገልጾታል እንግዲህ ያላመኑበትን እንዴት አድርገው ይጠሩታል ? ባልሰሙት ስ እንዴት ያምናሉ ? ያለ ሰባኪስ እንዴት ይሰማሉ ? መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው ተብሎ እንደ ተጻፈ ካልተላኩ እንዴት ይሰብካሉ ? ሮሜ 10 ፥ 14 እና 15 ጳውሎስ እንደተናገረው ከእግዚአብሔር በትክክል የተላከ በእርግጠኝነት መናገር አለበት የእርሱ ታማኝ አገልጋይ ለእግዚአብሔር ቃል ታማኝ ሆኖ ሕጉን ካላስተማረ ለእግዚአብሔር መታዘዝ ምን እንደሆነ ካልተናገረ ንስሐ የሚገባው ሰው ኃጢአትን አያቆምም የእግዚአብሔርንም ሕግ ይጥሳል ወይንም ይተላለፋል ኃጢአትን የሚያደርግ ሁሉ ዓመጽን ደግሞ ያደርጋል ኃጢአትም ዓመጽ ነው 1 ኛ ዮሐንስ 3 ፥ 4 ከዚሁ ጋር በማያያዝ በመጠራትና በመመረጥ መካከል ያለውን ል...

ሁሉም ሰው በእርግጠኝነት ንስሐ መግባት አለበት All must repent ክፍል አምስት ( ለ )

Image
ሁሉም ሰው በእርግጠኝነት ንስሐ መግባት አለበት   All must repent ክፍል አምስት ( ለ ) እግዚአብሔር ንስሐ በሚገባ ሕይወት እንደሚደሰት ሁሉ ንስሐ በማይገባ ሕይወት ደግሞ ያዝናል በማርቆስ ወንጌል 8 ፥ 22 _ 26 ላይ ወደ ቤተ ሳይዳም መጡ ዕውርም አመጡለት፥ እንዲዳስሰውም ለመኑት ዕውሩንም እጁን ይዞ ከመንደር ውጭ አወጣው፥ በዓይኑም ተፍቶበት እጁንም ጭኖበት አንዳች ታያለህን ? ብሎ ጠየቀው አሻቅቦም፦ ሰዎች እንደ ዛፍ ሲመላለሱ አያለሁ አለ ከዚህም በኋላ ደግሞ እጁን በዓይኑ ላይ ጫነበት አጥርቶም አየና ዳነም ከሩቅም ሳይቀር ሁሉን ተመለከተ ወደ ቤቱም ሰደደውና፦ ወደ መንደሩ አትግባ በመንደሩም ለማንም አንዳች አትናገር አለው ይለናል የተወደዳችሁ ወገኖች እንግዲህ ይህንን ዓይነ ሥውር ከመንደሩ ውጪ አውጥቶ ለምን ዓይኑን ሊፈውሰው ቻለ ? እንደገናም ጌታችን ኢየሱስ አጥርቶ እንዲያይ ካደረገው በኋላ ወደ መንደሩ አትግባ በመንደሩም ለማንም አንዳች አትናገር ለምን ሊለው ወደደ ? መንደሩ ጋር ያለው ችግር ምንድርነው ? ማለት የቤተ ሳይዳው ችግር ምንድነው ? ስንል በሉቃስ ወንጌል 10 ፥ 13 ላይ ወዮልሽ ኮራዚን፥ ወዮልሽ ቤተ ሳይዳ፤ በእናንተ የተደረገው ተአምራት በጢሮስና በሲዶና ተደርጎ ቢሆን፥ ማቅ ለብሰው በአመድም ተቀምጠው ከብዙ ጊዜ በፊት ንስሐ በገቡ ነበር የሚል ቃል ተጽፎ እናገኛለን ከዚህ የተነሳ ቤተ ሳይዳ ወደ እግዚአብሔር ምሕረት እንድትመጣ በተደረገው ...