በንቃት መጽሐፍቅዱስን ማንበብና ማጥናት Actively Read and Study the Bible ክፍል አንድ

በንቃት መጽሐፍቅዱስን ማንበብና ማጥናት


Actively Read and Study the Bible


ክፍል አንድ


የእውነትን ቃል በቅንነት የሚናገር የማያሳፍርም ሠራተኛ ሆነህ፥ የተፈተነውን ራስህን ለእግዚአብሔር ልታቀርብ ትጋ  2 ጢሞቴዎስ 2 15 እንደገናም በኤፌሶን 1 13 ላይ እናንተም ደግሞ የእውነትን ቃል፥ ይኸውም የመዳናችሁን ወንጌል፥ ሰምታችሁ ደግሞም በክርስቶስ አምናችሁ፥ በተስፋው መንፈስ በመንፈስ ቅዱስ ታተማችሁ ይለናል በመሆኑም መጽሐፍቅዱሳችንን በንቃት ከምንጊዜውም በተለየ ሁኔታ የምናጠናበት ምክንያት ቃሉ የእውነት ቃልና የመዳን ቃል ስለሆነ ነው ታድያ ይህ የእውነት ቃልም ሆነ የመዳን ቃል አምነን ስንከተለው እንድንሆንለት የሚፈልገው ነገርና የሚያደርገንም ነገር አለ እንድንሆንለት የሚፈልገው ነገር ቃሉን በቅንነት የምንናገርና የማናሳፍር ሠራተኛ ሆነን የተፈተነውን ራሳችንን ለእግዚአብሔር ልናቀርብ መትጋት የሚያደርገን  ነገር ደግሞ ይህንን የእውነትን ቃልና የመዳንን ወንጌል ሰምቶ መቅረት ብቻ ሳይሆን ሰምቶ በክርስቶስ በማመን በተስፋው መንፈስ በመንፈስ ቅዱስ መታተም ነው  ታድያ ይህ  ሊሆን የሚችለው ግን  በንቃት መጽሐፍቅዱስን ማንበብና ማጥናት ስንችል ነው ከዚህም ሌላ ይሄ የእውነት ቃል ለፍጥረቱ የበኲራት ዓይነት እንድንሆን መንፈሳዊ ልደትን የሚሰጠን  ነው ለዚህም ነው በያዕቆብ 1 18 ላይ ለፍጥረቱ የበኵራት ዓይነት እንድንሆን በእውነት ቃል አስቦ ወለደን የሚለን በመሆኑም በቆላስያስ 1 15 ላይ እርሱም የማይታይ አምላክ ምሳሌ ነው የሚታዩትና የማይታዩትም፥ ዙፋናት ቢሆኑ ወይም ጌትነት ወይም አለቅነት ወይም ሥልጣናት፥ በሰማይና በምድር ያሉት ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋልና ከፍጥረት ሁሉ በፊት በኵር ነው ሁሉ በእርሱና ለእርሱ ተፈጥሮአል ስለዚህ ይሄ ጌታ ለፍጥረቱ የበኵራት ዓይነት እንድንሆን በእውነት ቃል አስቦ የወለደን ብቻ ሳይሆን በሰማይና በምድር ያሉት ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋል ስለሚለን  ሁሉ በእርሱና ለእርሱ ተፈጥረዋል ስለሆነም መጽሐፍቅዱሳችንን በንቃት ስናነብና ስናጠና እንግዲህ ይህ የእውነት ቃል የሥነፍጥረት ፈጣሪና መገኛ መሆኑን የበኲራት ዓይነት የሆንበትን መንፈሳዊ ልደት አስገኚ መሆኑንም ጭምር እናይበታለን ለዚህም ነው ጊዜያችንን በእቅድና በመደበኛነት አስተካክለን በንቃት መጽሐፍቅዱሳችንን ለማንበብና ለማጥናት የተዘጋጀን እንድንሆን የሚያስፈልገን እንግዲህ እንደ ጥበበኞች እንጂ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንዴት እንድትመላለሱ በጥንቃቄ ተጠበቁ ቀኖች ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ ስለዚህ የጌታ ፈቃድ ምን እንደሆነ አስተውሉ እንጂ ሞኞች አትሁኑ ሲል ሐዋርያው የጻፈልን ኤፌሶን 5 15 _ 17 በጊዜና በእቅድ ውስጥ ሆኖ በመደበኛነት መጽሐፍቅዱሱን በንቃት ለማንበብና ለማጥናት የሚተጋ ሰው ጥበበኛና እንዴት እንዲመላለስ የተጠበቀ የቀኖችን ክፋት የሚያውቅ የጌታን ፈቃድ ያስተዋለ ነው ይህ ሰው እንዲህ ሲሆን ታድያ ዘመኑን ሳይቀር እየዋጀ በውጪ ባሉት ዘንድ በጥበብ ጭምር የሚመላለስ ነው ቆላስያስ 4 5 መጽሐፍቅዱሳችን አሁንም በኤፌሶን 5 10 ላይ እንግዲህ እንደ ጥበበኞች እንጂ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንዴት እንድትመላለሱ በጥንቃቄ ተጠበቁ ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ እያለን በተደጋጋሚ የሚናገረን ለዚህ ነው ጌታ በምናነበው ቃል ይባርከን ተባረኩልኝ


ለተጨማሪ እነዚህን ሃሳቦች በእንግሊዝኛም ጭምር በጥቂቱ  አብራራቸዋለሁ እና ተከታተሉ
1-          Actively Read and study the Bible
2-       Plan time for regular study

It`s easy to let everyday concerns interfere so schedule study time and try to maintain it. Over time you will look forward to this daily experience.

Servant of Lord Priest and Preacher Yonas Getaneh


Comments

Popular posts from this blog

024 ጋብቻ የቤተሰብ መሠረት ነው PART TWO እውነተኛ የምትወደድ ሴት ስትገኝና ኃላፊነት የሚሰማው ባል ሲገኝ ጋብቻ የቤተሰብ መሠረት ይሆናል ምሳሌ 18 ፥ 22 ፤ መዝሙር (128 )፥ 3 _ 4 ጋብቻችን የተበላሸ በሚሆንበት ጊዜ ህብረተሰብን ያልተወሰኑ ሥልጣኔዎችን ግንባታ ያግዳል ማኅበረሰብ ጠንካራ የሚሆነው በጋብቻና በቤተሰብ ውስጥ ነው በባልና በሚስት መካከል የተሻለ መረዳት ጥልቅ የፍቅር ግንኙነት ሊኖር ይገባል [ የተባረኩ ልጆች ይፈራሉና ] ዘፍጥረት 2 ፥ 24 ፤ ሮሜ 7 ፥ 2 _ 3 ፤ ኤፌሶን 5 ፥ 25 _ 32 ፤ ኤፌሶን 2 ፥ 19 _ 22 ፤ ሚልክያስ 2 ፥ 15 It was designed to be a lifelong relationship ( Romans 7 : 2 _ 3 ) that would produce godly children ( Malachi 2 : 15 ) በደስታ የሚኖሩ ተጋቢዎች አንዱና ትልቁ የእግዚአብሔር በረከት ተጋቢዎቹ የደስታ ሕይወት ውስጥ መግባታቸው ነው መክብብ 9 ፥ 9 እግዚአብሔር ዲዛይን ያደረገው ጋብቻ ተጋቢዎቹ በደስታ እንዲኖሩ የሚያደርግ ጋብቻ ነው ዘፍጥረት 2 ፥ 24 ሁለት ተጋቢዎች የጋብቻን ቀለበት ሲለዋወጡ የረጅም ጊዜ ቃልኪዳን መግባታቸው ነው A lifelong commitment. Biblically speaking ,this is a covenant a solemn promise to God and one`s mate to be faithful በመጽሐፍቅዱስ አነጋገር የተከበረ ቃልኪዳን የሚባለው ተጋቢዎቹ አንድ ጊዜ ታማኝ የሆኑበት ጉዳይ ነው የተወደዳችሁ ቅዱሳን ወገኖች ትምህርቱ በእነዚህ ሃሳቦች ዙርያ የተካተተ በመሆኑ በኦዲዮ የተለቀቁትን ቀጣይና ተከታታይ የሆኑ ትምህርቶች በመስማት እንድትባረኩበት ለእናንተ ለአድማጮች አቅርበነዋል ጌታ ዘመናችሁን ይባርክ የJoshua Breakthrough Renewal Teaching and Preaching Ministry አገልጋይና ባለ ራዕይ ቀሲስ ዮናስ ጌታነህ

የጌታ እራት ክፍል ሦስት

የመልእክት ርዕስ የሰዎችን ሥራም ሆነ የሥራ ጅማሬን ማወቅ ልታዋርደውም ጀመረች ኃይሉም ከእርሱ ሄደ (መሣፍንት 16 ፥ 9 ) ክፍል አንድ