Only those drown by God will understand እነዚህ ብቻ በእግዚአብሔር የፈቃድ መረዳት የተሳሉ ናቸው ክፍል ስድስት

Only those drown by God will understand



እነዚህ ብቻ በእግዚአብሔር የፈቃድ መረዳት የተሳሉ ናቸው


ክፍል ስድስት


ለእግዚአብሔር የመጠራትና የመመረጥ ሂደት ከእግዚአብሔር " በተአምር" መለየት የሚጀምር ነው መጽሐፉም  የላከኝ አብ ከሳበው በቀር ወደ እኔ ሊመጣ የሚችል የለም እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሳዋለሁ ይለናል ዮሐንስ ወንጌል 6 44  ከዚህም ሌላ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 6 65 ላይም ከአብ የተሰጠው ካልሆነ ወደ እኔ ሊመጣ የሚችል የለም አለን ጌታ እግዚአብሔር አስደናቂ የሆነና ያልተለመደ የኃይል ምስክርነት አለው እርሱ ለእኛ ደርሶ እኛን ከሰይጣን እስራት ተጽዕኖ ፣ ከምንኖርበትም ከዓለም ክፋት ፈትቶናል ወደፊትም ገና ብዙዎችን ይፈታል እግዚአብሔር የሚጋብዘን ከእነዚህ ነገሮች ሊያወጣን ነው ልባችንንም የሚለውጠው ወደ ራሱ አቅጣጫ ነው እርሱ አጥብቆ የሚፈልገው ማረጋገጫ እና እውቅናም የሰጠን የሚሰጠንም መንገዱን እንድንማር ፈቃዳችንንም ለእርሱ እንድናስገዛ ነው ነገር ግን ዝንባሌያችን ለእግዚአብሔር ሕግ ሊገዛ አይፈቅድም ሕጉንም መቃወም ይጀምራል በሮሜ 8 7 ላይ እንዲህ የሚል ቃል ተጽፎአል ስለ ሥጋ ማሰብ በእግዚአብሔር ዘንድ ጥል ነውና ለእግዚአብሔር ሕግ አይገዛምና መገዛትም ተስኖታል ይለናል ለእግዚአብሔር ፈቃድ መሸነፍ መማረክ በእውነትም ተአምር ነው መጽሐፍቅዱሳችን አሁንም ስለበጎ ፈቃዱ መፈለግንም ማድረግንም በእናንተ የሚሠራ እግዚአብሔር ነውና ይለናል ፊልጵስዩስ 2 13 ስለ አራቱ የመሬት ዓይነቶች ትርጉማቸው ለእግዚአብሔር ቃል ዘር ሰዎች ያላቸው ኃላፊነት የእግዚአብሔር ቃል እውነት በእነዚህ ነገሮች ውስጥ መሰበኩ ነገር ግን እግዚአብሔር የጠራቸው ብቻ እውነትን መረዳታቸውና መያዛቸው ለዚህ መልዕክት ሰዎች ልዩ ልዩ ምላሽ መስጠታቸው በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 13 ላይ በግልጽ ተጽፎ እናገኘዋለን በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 13 ቊጥር 19 ላይ ደግሞ የመንግሥትን ቃል ሰምቶ በማያስተውል ክፉ ይመጣል በልቡ የተዘራውንም ይነጥቃል በመንገድ ዳር የተዘራው ይህ ነው ይለናል ታድያ እንደነዚህ ዓይነት ሕዝቦች የመልዕክቱን አስፈላጊነት አያስተውሉም  በመሆኑም ይህን መልዕክትና ትምህርት ያነበብን የደረሰንም ሰዎች ያነበብነው ቃል ተራ የሆኑና ሰዎችን ለማሳመንም ሆነ የራስ ለማድረግ ሲባል ተኰልኩለው የተጻፉ ልብ ወለድ የሰዎች የፈጠራ ድርሰቶች  ሳይሆኑ የእግዚአብሔር የመንግሥቱ ቃል ስለሆነ የመልዕክቱን አስፈላጊነት አስተውለን እኛም ለየራሳችን  አወንታዊ ምላሽ ልንሰጥበት ይገባል  ስል ወንድማዊ ምክሬን ላስተላልፍላችሁ እወዳለሁ ጌታ እግዚአብሔር በምናነበው ቃል ዓይኖቻችንን ይክፈትልን አሜን
የ Joshua Breakthrough Renewal Teaching and Preaching Ministry  


አገልጋይና ባለራዕይ ቀሲስ ዮናስ ጌታነህ

Comments

Popular posts from this blog

024 ጋብቻ የቤተሰብ መሠረት ነው PART TWO እውነተኛ የምትወደድ ሴት ስትገኝና ኃላፊነት የሚሰማው ባል ሲገኝ ጋብቻ የቤተሰብ መሠረት ይሆናል ምሳሌ 18 ፥ 22 ፤ መዝሙር (128 )፥ 3 _ 4 ጋብቻችን የተበላሸ በሚሆንበት ጊዜ ህብረተሰብን ያልተወሰኑ ሥልጣኔዎችን ግንባታ ያግዳል ማኅበረሰብ ጠንካራ የሚሆነው በጋብቻና በቤተሰብ ውስጥ ነው በባልና በሚስት መካከል የተሻለ መረዳት ጥልቅ የፍቅር ግንኙነት ሊኖር ይገባል [ የተባረኩ ልጆች ይፈራሉና ] ዘፍጥረት 2 ፥ 24 ፤ ሮሜ 7 ፥ 2 _ 3 ፤ ኤፌሶን 5 ፥ 25 _ 32 ፤ ኤፌሶን 2 ፥ 19 _ 22 ፤ ሚልክያስ 2 ፥ 15 It was designed to be a lifelong relationship ( Romans 7 : 2 _ 3 ) that would produce godly children ( Malachi 2 : 15 ) በደስታ የሚኖሩ ተጋቢዎች አንዱና ትልቁ የእግዚአብሔር በረከት ተጋቢዎቹ የደስታ ሕይወት ውስጥ መግባታቸው ነው መክብብ 9 ፥ 9 እግዚአብሔር ዲዛይን ያደረገው ጋብቻ ተጋቢዎቹ በደስታ እንዲኖሩ የሚያደርግ ጋብቻ ነው ዘፍጥረት 2 ፥ 24 ሁለት ተጋቢዎች የጋብቻን ቀለበት ሲለዋወጡ የረጅም ጊዜ ቃልኪዳን መግባታቸው ነው A lifelong commitment. Biblically speaking ,this is a covenant a solemn promise to God and one`s mate to be faithful በመጽሐፍቅዱስ አነጋገር የተከበረ ቃልኪዳን የሚባለው ተጋቢዎቹ አንድ ጊዜ ታማኝ የሆኑበት ጉዳይ ነው የተወደዳችሁ ቅዱሳን ወገኖች ትምህርቱ በእነዚህ ሃሳቦች ዙርያ የተካተተ በመሆኑ በኦዲዮ የተለቀቁትን ቀጣይና ተከታታይ የሆኑ ትምህርቶች በመስማት እንድትባረኩበት ለእናንተ ለአድማጮች አቅርበነዋል ጌታ ዘመናችሁን ይባርክ የJoshua Breakthrough Renewal Teaching and Preaching Ministry አገልጋይና ባለ ራዕይ ቀሲስ ዮናስ ጌታነህ

የጌታ እራት ክፍል ሦስት

የመልእክት ርዕስ የሰዎችን ሥራም ሆነ የሥራ ጅማሬን ማወቅ ልታዋርደውም ጀመረች ኃይሉም ከእርሱ ሄደ (መሣፍንት 16 ፥ 9 ) ክፍል አንድ