001 የትምህርት ርዕስ ለጋብቻ ያለ መሠረት Part one  በጋብቻ ውስጥ ያለ ጠንካራ ግንኙነትን መመስረትና መገንባት የሚቻለው ሁለቱም ተጋቢዎች የሆኑ ባልና ሚስት በጣም በፍጥነት የእግዚአብሔርን ሕግ መቀበልና መለማመድ ሲችሉ ነው  የእግዚአብሔርን ሕግ ስንቀበልና ስንለማመድ ደግሞ ጋብቻችንን ከመመስረትና ከመገንባት ባሻገር ካለፈውም ኃጢአት ተመልሰን እግዚአብሔርን መታዘዝ እንጀምራለን በዚህ ውስጥም ዘላለማዊ የሆነውን የእግዚአብሔርን ደስታ እናገኛለን ሕዝቅኤል 18 ፥ 21 ፤ የሐዋርያት ሥራ 2 ፥ 36 ፤ የሐዋርያት ሥራ 26 ፥ 18  ጌታ እግዚአብሔር ከባልና ሚስቱ ከእያንዳንዳቸው ለእርሱ የሚጠብቀው በሚያሳስበው በጋብቻ ፈተናዎቻቸው ውስጥ የሚሰጡትን ምላሽ ነው  መጽሐፉም በጎ ለማድረግ አውቆ ለማይሠራው ኃጢአት ነው ይለናልና ያዕቆብ 4 ፥ 17  እንደገናም ቢቻል ሁለቱ ባይቻል ግን ከሁለቱ አንዱ ማለትም ባል አለበለዚያም ሚስት ሕይወታቸውን ለእግዚአብሔርና ለእግዚአብሔር መለኪያ ከሰጡ እግዚአብሔር አምላክ ሁለቱንም ተጋቢዎች ሊባርካቸው በር ይከፍታል 1ኛ ቆሮንቶስ 7 ፥ 13 _ 14  እርግጠኛና የማያጠራጥር ፍቅር ለእግዚአብሔር የመታዘዝ ምሳሌ ነው በባል ወይም በሚስት ባለ ተጽእኖ እግዚአብሔርን ማስደሰት መፈለግ ይመጣል 1ኛ ጴጥሮስ 3 ፥ 1 _ 4  አንድ ሰው ልዩነት ሊያመጣ ይችላልና One person can make a difference የተወደዳችሁ ወገኖች ትምህርቶቹ እንግዲህ በእነዚህና በመሳሰሉት ሃሳቦች የተጠቃለሉ ናቸው ከዚህ በመቀጠል ይህንኑ በሰፊው የሚያብራራ በኦዲዮ የተለቀቀ ትምህርት ስላለ ይህንኑ በተከታታይ የቀረበ ትምህርት ሳያመልጥዎ እንዲከታተሉ በጌታ ፍቅር ልናሳስብዎ እንወዳለን የጌታ ሰላም ከሁላችን ጋር ይሁን የJoshua Breakthrough Renewal Teaching and Preaching Ministry አገልጋይና ባለ ራዕይ ቀሲስ ዮናስ ጌታነህ

Comments

Popular posts from this blog

024 ጋብቻ የቤተሰብ መሠረት ነው PART TWO እውነተኛ የምትወደድ ሴት ስትገኝና ኃላፊነት የሚሰማው ባል ሲገኝ ጋብቻ የቤተሰብ መሠረት ይሆናል ምሳሌ 18 ፥ 22 ፤ መዝሙር (128 )፥ 3 _ 4 ጋብቻችን የተበላሸ በሚሆንበት ጊዜ ህብረተሰብን ያልተወሰኑ ሥልጣኔዎችን ግንባታ ያግዳል ማኅበረሰብ ጠንካራ የሚሆነው በጋብቻና በቤተሰብ ውስጥ ነው በባልና በሚስት መካከል የተሻለ መረዳት ጥልቅ የፍቅር ግንኙነት ሊኖር ይገባል [ የተባረኩ ልጆች ይፈራሉና ] ዘፍጥረት 2 ፥ 24 ፤ ሮሜ 7 ፥ 2 _ 3 ፤ ኤፌሶን 5 ፥ 25 _ 32 ፤ ኤፌሶን 2 ፥ 19 _ 22 ፤ ሚልክያስ 2 ፥ 15 It was designed to be a lifelong relationship ( Romans 7 : 2 _ 3 ) that would produce godly children ( Malachi 2 : 15 ) በደስታ የሚኖሩ ተጋቢዎች አንዱና ትልቁ የእግዚአብሔር በረከት ተጋቢዎቹ የደስታ ሕይወት ውስጥ መግባታቸው ነው መክብብ 9 ፥ 9 እግዚአብሔር ዲዛይን ያደረገው ጋብቻ ተጋቢዎቹ በደስታ እንዲኖሩ የሚያደርግ ጋብቻ ነው ዘፍጥረት 2 ፥ 24 ሁለት ተጋቢዎች የጋብቻን ቀለበት ሲለዋወጡ የረጅም ጊዜ ቃልኪዳን መግባታቸው ነው A lifelong commitment. Biblically speaking ,this is a covenant a solemn promise to God and one`s mate to be faithful በመጽሐፍቅዱስ አነጋገር የተከበረ ቃልኪዳን የሚባለው ተጋቢዎቹ አንድ ጊዜ ታማኝ የሆኑበት ጉዳይ ነው የተወደዳችሁ ቅዱሳን ወገኖች ትምህርቱ በእነዚህ ሃሳቦች ዙርያ የተካተተ በመሆኑ በኦዲዮ የተለቀቁትን ቀጣይና ተከታታይ የሆኑ ትምህርቶች በመስማት እንድትባረኩበት ለእናንተ ለአድማጮች አቅርበነዋል ጌታ ዘመናችሁን ይባርክ የJoshua Breakthrough Renewal Teaching and Preaching Ministry አገልጋይና ባለ ራዕይ ቀሲስ ዮናስ ጌታነህ

የጌታ እራት ክፍል ሦስት

የመልእክት ርዕስ የሰዎችን ሥራም ሆነ የሥራ ጅማሬን ማወቅ ልታዋርደውም ጀመረች ኃይሉም ከእርሱ ሄደ (መሣፍንት 16 ፥ 9 ) ክፍል አንድ