Yonas Asfaw : የመናኙ ሰው ዕድል ፈንታው ክርስቶስ ሆነ Part Two Get link Facebook X Pinterest Email Other Apps December 11, 2014 Yonas Asfaw : የመናኙ ሰው ዕድል ፈንታው ክርስቶስ ሆነ Part Two: የመናኙ ሰው ዕድል ፈንታው ክርስቶስ ሆነ Part Two የተወደዳችሁ ወገኖች የአባ ዘውዱ ኪዳኑን ምስክርነት ክፍል አንድ ማቅረቤ ይታወሳል ክፍል ሁለ... Get link Facebook X Pinterest Email Other Apps Comments
024 ጋብቻ የቤተሰብ መሠረት ነው PART TWO እውነተኛ የምትወደድ ሴት ስትገኝና ኃላፊነት የሚሰማው ባል ሲገኝ ጋብቻ የቤተሰብ መሠረት ይሆናል ምሳሌ 18 ፥ 22 ፤ መዝሙር (128 )፥ 3 _ 4 ጋብቻችን የተበላሸ በሚሆንበት ጊዜ ህብረተሰብን ያልተወሰኑ ሥልጣኔዎችን ግንባታ ያግዳል ማኅበረሰብ ጠንካራ የሚሆነው በጋብቻና በቤተሰብ ውስጥ ነው በባልና በሚስት መካከል የተሻለ መረዳት ጥልቅ የፍቅር ግንኙነት ሊኖር ይገባል [ የተባረኩ ልጆች ይፈራሉና ] ዘፍጥረት 2 ፥ 24 ፤ ሮሜ 7 ፥ 2 _ 3 ፤ ኤፌሶን 5 ፥ 25 _ 32 ፤ ኤፌሶን 2 ፥ 19 _ 22 ፤ ሚልክያስ 2 ፥ 15 It was designed to be a lifelong relationship ( Romans 7 : 2 _ 3 ) that would produce godly children ( Malachi 2 : 15 ) በደስታ የሚኖሩ ተጋቢዎች አንዱና ትልቁ የእግዚአብሔር በረከት ተጋቢዎቹ የደስታ ሕይወት ውስጥ መግባታቸው ነው መክብብ 9 ፥ 9 እግዚአብሔር ዲዛይን ያደረገው ጋብቻ ተጋቢዎቹ በደስታ እንዲኖሩ የሚያደርግ ጋብቻ ነው ዘፍጥረት 2 ፥ 24 ሁለት ተጋቢዎች የጋብቻን ቀለበት ሲለዋወጡ የረጅም ጊዜ ቃልኪዳን መግባታቸው ነው A lifelong commitment. Biblically speaking ,this is a covenant a solemn promise to God and one`s mate to be faithful በመጽሐፍቅዱስ አነጋገር የተከበረ ቃልኪዳን የሚባለው ተጋቢዎቹ አንድ ጊዜ ታማኝ የሆኑበት ጉዳይ ነው የተወደዳችሁ ቅዱሳን ወገኖች ትምህርቱ በእነዚህ ሃሳቦች ዙርያ የተካተተ በመሆኑ በኦዲዮ የተለቀቁትን ቀጣይና ተከታታይ የሆኑ ትምህርቶች በመስማት እንድትባረኩበት ለእናንተ ለአድማጮች አቅርበነዋል ጌታ ዘመናችሁን ይባርክ የJoshua Breakthrough Renewal Teaching and Preaching Ministry አገልጋይና ባለ ራዕይ ቀሲስ ዮናስ ጌታነህ July 30, 2015 Read more
የጌታ እራት ክፍል ሦስት July 01, 2015 የጌታ እራት ክፍል ሦስት በዚህ ክፍለ ትምህርት የጌታን እራት የምንጠቀመው በ1ኛ ቆሮንቶስ 11 ፥ 20 በተጻፈው ቃል መሠረት ሲሆን የጌታን እራት በምንካፈልበት ጊዜ ዓላማው ከጌታ ኃይልንና ጥንካሬን መቀበላችንን እንድናውቅ የሚያስችለን ነው እንደገናም ራሳችን ለጌታ የተሰጠን እንድንሆን ለማድረግ ነው ይህንን የጌታን እራት ስንወስድ ቅዱስ ቁርባን ወይንም በእንግሊዘኛው Holy Communion ( ሆሊኮሚኑየን ) መሆኑን እንረዳለን ከዚህም ሌላ መጽሐፍቅዱሳችን እንደሚያስተምረን ከግሪኩ ቃል የተነሳ ምስጋናም የምንሰጥበት ነው በሉቃስ ወንጌል 22 ፥ 17 _ 19 ላይ ጽዋንም ተቀበለ አመስግኖም ይህን እንካችሁ በመካከላችሁም ተካፈሉት እላችኋለሁና፥ የእግዚአብሔር መንግሥት እስክትመጣ ድረስ ከአሁን ጀምሮ ከወይኑ ፍሬ አልጠጣም አለ እንጀራንም አንሥቶ አመሰገነ ቆርሶም ሰጣቸውና ስለ እናንተ የሚሰጠው ሥጋዬ ይህ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ ይለናል እንደገናም በ1ኛ ቆሮንቶስ 11 ፥ 24 _ 25 ላይ ጌታ ኢየሱስ አልፎ በተሰጠበት በዚያች ሌሊት እንጀራን አንሥቶ አመሰገነ፥ ቆርሶም እንካችሁ ብሉ፤ ይህ ስለ እናንተ የሚሆን ሥጋዬ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ እንደዚሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን ደግሞ አንሥቶ ይህ ጽዋ በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው፤ በጠጣችሁት ጊዜ ሁሉ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ ይለናል ስለዚህ ቅዱሳን ወገኖች ሳይመሰገን የተሰጠን የጌታ እራት የለምና እኛም ... Read more
የመልእክት ርዕስ የሰዎችን ሥራም ሆነ የሥራ ጅማሬን ማወቅ ልታዋርደውም ጀመረች ኃይሉም ከእርሱ ሄደ (መሣፍንት 16 ፥ 9 ) ክፍል አንድ February 09, 2016 የመልእክት ርዕስ የሰዎችን ሥራም ሆነ የሥራ ጅማሬን ማወቅ ልታዋርደውም ጀመረች ኃይሉም ከእርሱ ሄደ ( መሣፍንት 16 ፥ 9 ) ክፍል አንድ የመልእክት ርዕስ የሰዎችን ሥራም ሆነ የሥራ ጅማሬን ማወቅ ልታዋርደውም ጀመረች ኃይሉም ከእርሱ ሄደ ( መሣፍንት 16 ፥ 9 ) ክፍል አንድ የተወደዳችሁ ወገኖች በቅድሚያ የጌታ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ ዛሬ በዚህ መልዕክት ወደ እናንተ መጥቻለሁ ይህንን መልዕክት አንብባችሁ እንድትጠቀሙበትና ለሌሎችም ሼር እንድታደርጉት በጌታ ፍቅር ለማሳሰብ እወዳለሁ ተባረኩልኝ ይህንን መልዕክት በደሊላና በሶምሶን ታሪክ ጀምሬዋለሁ እንደምትመለከቱትና ከላይም በመግቢያዬ ላይ እንደገለጽኩት ደሊላ ሶምሶንን ልታዋርደው ጀመረች ኃይልም ከእርሱ ሄደ ይለናል ይህ እንግዲህ ደሊላ በትክክል ሥራዋን የጀመረችበት ጊዜ ነው ለማለት እንችላለን ታድያ ይህንን የጅማሬ ጊዜ ነው ሶምሶን በውል ያላወቀው ደሊላ ከሶምሶን ጋር በቆየችባቸው ጊዜያት ለሶምሶን ደሊላ ትክክለኛውን ሥራ የጀመረችበት ጊዜ መስሎታል አይደለም ለሶምሶን ለሁላችንም ቢሆን ደሊላ ከሶምሶን ጋር በተገናኘችባቸው ጊዜያቶች ሁሉ ከድርጊቶችዋና ከሁኔታዎችዋም የተነሳ በሰላም አብራ ስለምትወጣ ስለምትገባ ከአንደበትዋ ልስላሴና አነጋገር ከምታሳየውም አቀራረብና የአነጋገር ዘዬ ሥራዋን በትክክል የጀመረች ብቻ ሳይሆን በአግባብ ሥራዋን በመስራት ላይ ያለችና የሚገባትንም ... Read more
Comments
Post a Comment