Posts

Showing posts from April, 2015

Seeking Guidance የሚመራ መፈለግ በመታዘዝ የሚመጡ ብዙ ትርፎች በበራችን ላይ በፍጥነት ለእኛ ይገለጣሉ ክፍል ስድስት

Seeking Guidance  የሚመራ መፈለግ  በመታዘዝ የሚመጡ ብዙ ትርፎች በበራችን ላይ በፍጥነት ለእኛ ይገለጣሉ ክፍል ስድስት የእግዚአብሔር ቃል በመዝሙር 34 ፥ 8 ላይ እግዚአብሔር ቸር እንደሆነ ቅመሱ   እዩም በእርሱ የሚታመን ሰው ምስጉን ነው አለ ስለዚህ የእግዚአብሔርን ቸርነት ለመቅመስ የእግዚአብሔርን ቃል መታዘዝ አማራጭ የሌለው ነገር ነው በ1ኛ ዮሐንስ 3 ፥ 22 ላይ የእግዚአብሔር ቃል የሚለን እንደዚህ ነው ወዳጆች ሆይ ልባችን ባይፈርድብን በእግዚአብሔር ዘንድ ድፍረት አለን ትእዛዙንም የምንጠብቅና በፊቱ ደስ የሚያሰኘውን የምናደርግ ስለሆንን የምንለምነውን ሁሉ ከእርሱ እናገኛለን ይለናል በመሆኑም እንግዲህ ለቃሉ በመታዘዝ ውስጥ የሚፈለገው ነገር ሁሉ ከተገኘ በመታዘዝ የሚመጡ ብዙ ትርፎች እንዳሉን በዚሁ በተገለጠው በእግዚአብሔር ቃል መረዳት እንችላለን በትንቢተ ሚልክያስ 3 ፥ 10 ላይም በቤቴ ውስጥ መብል እንዲሆን አሥራቱን ሁሉ ወደ ጎተራ አግቡ የሰማይንም መስኮት ባልከፍትላችሁ በረከትንም አትረፍርፌ ባላፈስላችሁ   በዚህ ፈትኑኝ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ይለናል እኛ ጌታ በሚያዘን ነገር ሁሉ ታማኞች ሆነን ለቃሉ ከታዘዝን እግዚአብሔር በረከቱን ሁሉ ሊያፈስልን የታመነ ነው ለዚህ ነው ጌታ ኢየሱስም እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸው መጣሁ ያለው ዮሐንስ ወንጌል 10 ፥ 10 የሚበዛ ሕይወት ቃሉን ከመታዘዝ የተነሳ በእግዚአብሔር በረከ...

ሀ _ የቃሉ ተማሪ መሆን Become a student of the word Take not ክፍል አራት

Image
የሚመራ መፈለግ     Seeking Guidance       ሀ   _   የቃሉ ተማሪ መሆን       Become a student of the word       Take not       ክፍል አራት       እግዚአብሔር የቃሉ ተማሪ እንድንሆንለት ይፈልጋል በዘጸአት 4 ፥ 12 ላይ እንግዲህ አሁን ሂድ፥ እኔም ከአፍህ ጋር እሆናለሁ፥ የምትናገረውንም አስተምርሃለሁ አለው ይለናል በመጽሐፈ ኢዮብ 33 ፥ 33 ላይ ደግሞ ያለዚያም እኔን ስማ ዝም በል፥ እኔም ጥበብን አስተምርሃለሁ በመዝሙረ ዳዊት 32 ፥ 8 ላይም አስተምርሃለሁ በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ ዓይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ ይለናል ጌታ እግዚአብሔር ሊያስተምረን ሲፈልግና ሲያስተምረን ማድረግ የሚገባን ነገር በቅድሚያ ዝም ማለት ነው እንደገናም እርሱን መስማት ነው ያንጊዜ ከዚሁ ጌታ ጥበብን መማር ይሆንልናል ይህ በሚሆንበት ጊዜ በምንሄድበት መንገድ ሁሉ ይመራናል ዓይኖቹንም በእኛ ላይ ያጸናል ይህ ካልሆነ ግን ማለት እርሱ ሊያስተምረን ሲፈልግ እኛም ከእርሱ ልንማር ስንል   ዝም ማለት ካልቻልንና እርሱንም ለመስማት ካልወደድን ፍጹም የምንማረው ነገር አይኖርም እርሱም ዓይኖቹን በእኛ ላይ አያጸናም ማለት እን...